1 ሻምሺ-አዳድ
From Wikipedia, the free encyclopedia
1 ሻምሺ-አዳድ የተርቃ ንጉሥ ኢላ-ካብካቡ ልጅ ነበረ። «የማሪ ሊሙ ስሞች ዜና መዋዕል» (MEC) የተባለው ሰነድ እንደሚለን፣ የሻምሺ-አዳድ ልደት ኢናያ (ወይም ዳዳያ) ሊሙ በሆነበት ዓመት፣ 1760 ዓክልበ. ሆነ ።[1] በኋላ በሻሩም-አዳድ ሊሙነት (1745 ዓክልበ.) «ሻምሺ-አዳድ ያባቱን ቤት ገባ» ማለት እድሜው 15 ዓመት ሲሆን የተርቃን ዙፋን ወረሰ።
የሻምሺ-አዳድ ስም በዚህ ዜና መዋዕል ብዙ ጊዜ ይጠቀሳል። በ1734 ዓክልበ. ኡኒናን አሸነፈ፤ ለሚከተሉት ዓመታት ግን ከስሙ በቀር ቃላቱ ጠፍቷል። ወደ አሦር ንጉሥ ናራም-ሲን ዘመን መጨረሻ በአሦር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ ወደ «ካርዱንያሽ» (ባቢሎን) ወረደ። ይህ ማለት በዘመቻ ባቢሎንን ያዘ አይመስልም፤ ምናልባት ወደ ባቢሎን የሄደው በስደት ይሆናል። ሆኖም በ1723 ዓክልበ. ከባቢሎን ወጥቶ ኤካላቱምን እንደ ያዘ ይዘገባል። እዚያ ለ፫ ዓመታት ቆይቶ አሹርን ይዞ ንጉሡን 2 ኤሪሹምን አስወጥቶ የአሦርን መንግሥት ለራሱ ቃመው።
ከሻምሺ-አዳድ ዘመን በአሦር ጀምሮ የካሩም ንግድ በትንሹ እስያ ተመለሰ፤ በልጁም ዘመን እስከ 1678 ዓክልበ. ድረስ ተቀጠለ።