ሴሶስትሪስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ሴሶስትሪስ (ግሪክኛ፦ Σέσωστρις) በታሪክ ጸሐፊዎች ሄሮዶቶስ፣ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ፣ ስትራቦንና ማኔጦን የተጠቀሰ የግብጽ ፈርዖን ነበር።
ማኔጦን በ2 ሰኑስረት (ወይም ሰንዎስረት) እና በተከታዩ በ3 ሰኑስረት ፈንታ ለሁለቱ አንድ ስም ብቻ አለው፤ እሱም «ሴሶስትሪስ» ሲሆን ለ፵፰ ዓመታት እንደ ገዛ ይለናል። ፫ ሰኑስረት ቢያንስ በከነዓን እስከ ሴኬም ድረስ በ1884 ዓክልበ. አካባቢ እንደ ዘመተ ይታወቃል።